የእግዚአብሔርን ቃል መስበክና ማስተማር
የእግዚአብሔርን ቃል በታማኝነት እንሰብካለን፤ እናስተምራለን፤ ወንጌልንም ለሰዎች ሁሉ በግልጽነት፣ በእውነትና በፍቅር እናሰራጫለን።
“ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።”
ማርቆስ 16:15
አገልግሎታችን ከታላቁ ተልእኮ የመነጨ ነው። ከታች ያለው እያንዳንዱ መስክ በእግዚአብሔር ቃል ላይ የተመሠረተ ነው።
የእግዚአብሔርን ቃል በታማኝነት እንሰብካለን፤ እናስተምራለን፤ ወንጌልንም ለሰዎች ሁሉ በግልጽነት፣ በእውነትና በፍቅር እናሰራጫለን።
“ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።”
ማርቆስ 16:15
ሰዎችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግላዊ ግንኙነት እንመራለን፤ ድነትን፣ ለውጥንና አዲስ ሕይወትን እንዲለማመዱ እንረዳለን።
አማኞች መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያገኙ ትኩረት በመስጠት፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት፣ በጸሎትና በመንፈሳዊ ምክር ጠንካራ ደቀ መዛሙርትን እንገነባለን።
“ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ ... ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው።”
ማቴዎስ 28:19
አገልጋዮችና አብያተ ክርስቲያናት በጥሪአቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ስልጠና፣ ግብዓቶችና ድጋፍ እንዲሁም ስኮላርሺፕ በመስጠት እናበቃቸዋለን።
“ቅዱሳንን ለአገልግሎት ሥራ ለማዘጋጀት፣ የክርስቶስ አካል ይገነባ ዘንድ።”
ኤፌሶን 4:12
በአገልግሎት ላይ ያሉ አገልጋዮችን ድጋፍ በሚያስፈልጋቸው ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ቀርበን በማነጋገር ተገቢ የሆኑ ድጋፎችን እናደርጋለን።
በወንጌል ምክንያት ለስደትና ለችግር የሚጋለጡ ወንድሞችንና እህቶችን እናበረታለን፤ የሙያ ስልጠናና ስኮላርሺፕ በማመቻቸት ራሳቸውን እስኪችሉ ድረስ መጠለያና ምግብ የሚያገኙበትን ስፍራ እናዘጋጃለን።
“በእስር ላይ ያሉትን ከእነርሱ ጋር እንደ ታሰራችሁ ሆናችሁ አስቧቸው።”
ዕብራውያን 13:3
በአማኞችና በአብያተ ክርስቲያናት መካከል ፍቅርን፣ አንድነትንና ትብብርን እናበረታታለን፤ ለእግዚአብሔር መንግሥት አብረን እንሠራለን።
“በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።”
ኤፌሶን 4:3
ወንጌል ባልደረሰባቸው አካባቢዎች ሚስዮናውያንና አገልጋዮችን አዘጋጅተን እንልካለን፤ ከአብያተ ክርስቲያናት ጋር በመተባበር አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲተከሉ እናደርጋለን፤ መሪዎችን በማሳደግ የመንግሥቱን ራእይ እናስፋፋለን።