የመልካም መንገድ ዓለም አቀፍ የተልእኮ አገልግሎት
ምስክርነቶችና ዜናዎች

ለተሰደዱ ጎን መቆም

በወንጌል ምክንያት ለስደትና ለችግር የሚጋለጡ ብዙ ወንድሞችና እህቶች አሉ። እኛም እንደ ዕብራውያን 13:3 ቃል ከእነርሱ ጎን እንቆማለን።

የሙያ ስልጠና፣ ስኮላርሺፕ፣ መጠለያና ምግብ በማመቻቸት ራሳቸውን እስኪችሉ ድረስ እንረዳቸዋለን። በዚህ አገልግሎት አጋር ለመሆን ይችላሉ።