የእግዚአብሔርን ቃል መስበክና ማስተማር
የእግዚአብሔርን ቃል በታማኝነት እንሰብካለን፤ እናስተምራለን፤ ወንጌልንም ለሰዎች ሁሉ በግልጽነት፣ በእውነትና በፍቅር እናሰራጫለን።
ማርቆስ 16:15
አገልግሎቶቻችን
የእግዚአብሔርን ቃል በታማኝነት መስበክና ማስተማር፣ ሰዎችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ድነት መምራት፣ ጠንካራ ደቀ መዛሙርትንና ጤናማ አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት።
በቅዱስ ቃል ላይ የተመሠረቱ ስምንት የአገልግሎት መስኮች፤ በእነዚህም የክርስቶስን አካል እናገለግላለን፤ የጠፉትንም እንፈልጋለን።
የእግዚአብሔርን ቃል በታማኝነት እንሰብካለን፤ እናስተምራለን፤ ወንጌልንም ለሰዎች ሁሉ በግልጽነት፣ በእውነትና በፍቅር እናሰራጫለን።
ማርቆስ 16:15
ሰዎችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግላዊ ግንኙነት እንመራለን፤ ድነትን፣ ለውጥንና አዲስ ሕይወትን እንዲለማመዱ እንረዳለን።
አማኞች መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያገኙ ትኩረት በመስጠት፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት፣ በጸሎትና በመንፈሳዊ ምክር ጠንካራ ደቀ መዛሙርትን እንገነባለን።
ማቴዎስ 28:19
አገልጋዮችና አብያተ ክርስቲያናት በጥሪአቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ስልጠና፣ ግብዓቶችና ድጋፍ እንዲሁም ስኮላርሺፕ በመስጠት እናበቃቸዋለን።
ኤፌሶን 4:12
በአገልግሎት ላይ ያሉ አገልጋዮችን ድጋፍ በሚያስፈልጋቸው ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ቀርበን በማነጋገር ተገቢ የሆኑ ድጋፎችን እናደርጋለን።
በወንጌል ምክንያት ለስደትና ለችግር የሚጋለጡ ወንድሞችንና እህቶችን እናበረታለን፤ የሙያ ስልጠናና ስኮላርሺፕ በማመቻቸት ራሳቸውን እስኪችሉ ድረስ መጠለያና ምግብ የሚያገኙበትን ስፍራ እናዘጋጃለን።
ዕብራውያን 13:3
የእግዚአብሔር ቃል በዓለም ሁሉ እንዲደርስ፣ ሰዎች ወደ ክርስቶስ እንዲመጡ፣ ጠንካራ ደቀ መዛሙርት እንዲነሱ እና የእግዚአብሔር መንግሥት በትውልድ ሁሉ እንዲስፋፋ ማየት።
እንዲሁም በክርስቶስ ፍቅር የተመሠረተ አንድነት፣ ተስፋና ሕይወት የሞላበት፣ ለክርስቶስ ወንጌል የጨከነ ትውልድ መነሳትን ማየት።
የምናደርገውን ሁሉ የሚመሩ መሠረታዊ እምነቶቻችን።
በእግዚአብሔር ቃል እውነት መመራትና በታማኝነት መኖር።
ሁሉን በክርስቶስ ፍቅር መቀበልና ማገልገል።
በሁሉም ነገር እውነተኛና ታማኝ መሆን።
ራስን ዝቅ አድርጎ ሌሎችን በትሕትና ማገልገል።
በክርስቶስ አካል ውስጥ አንድነትንና ትብብርን ማጠንከር።
ሁሉን በጸሎት መጀመርና በእግዚአብሔር ማመን።
ለእግዚአብሔር ፈቃድ ታዛዥ መሆን።
ለደካሞችና ለተቸገሩ ርኅራኄ ማሳየት።
በአገልግሎት ሁሉ በጥራትና በትጋት መሥራት።
ከመስኩ የተገኙ ምስክርነቶችና ወቅታዊ መረጃዎች።
የመልካም መንገድ ዓለም አቀፍ የተልእኮ አገልግሎት ራእይ፣ ተልእኮና ጉዞ።
ምስክርነቱን ያንብቡበወንጌል ምክንያት ለችግር የተጋለጡ ወንድሞችንና እህቶችን እንዴት እንደምንደግፍ።
ምስክርነቱን ያንብቡ